
Fana Broadcasting Corporate
Fana Broadcasting Corporate, wishes to recruit applicants for the following vacant positions.
ክፍት የስራ ማስታወቂያ!
ድርጅታችን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ከዚህ በታች ለተመለከቱት ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
1. የስራ መደቡ መጠሪያ፡- ጀማሪ ኢንጂነር
ተፈላጊ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ፡- በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ፣ ኮሙኒኬሽን ኢንጂነሪንግ፤ ኤሌክትሮኒክስ፤ ኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ ወይም ተመሳሳይ የትምህርት መስክ ቢ.ኤ.ሲ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት
ብዛት – 7 /ሰባት/
የቅጥር ሁኔታ – በፍሪላንሰር /ኮንትራት/
2. የስራ መደቡ መጠሪያ፡- ጀማሪ የማስታወቂያ ክትትል
ባለሙያ
ተፈላጊ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ፡- በጋዜጠኝነት፣ በቋንቋና ስነ-ፅሑፍ፣ በኮሙኒኬሽን፣ በማርኬቲንግና ማኔጅመንት ተመሳሳይ የትምህርት መስክ ወይም በተዛማጅ የትምህርት መስክ ቢ.ኤ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት እና የምረቃ ጊዜ እ.ኤ.አ. ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ሆኖ CGPA ከ3 ነጥብ እና በላይ ያለው/ያላት
ደረጃ – V ብዛት – 1
የቅጥር ሁኔታ – በቋሚነት
ደመወዝ፡- በድርጅቱ ስኬል መሠረት
የስራ ቦታ፡- ዋናው መ/ቤት /አዲስ አበባ/
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ ከታህሳስ 19 እስከ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት በሰው ሀብት ስራ አመራር ቢሮ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ.ማ. – ( 0115 -51-67-77
አድራሻ፡- ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ